Tuesday, January 21, 2014

ለአቶ ተክሌ የሻዉ ሞረሽ ወገኔ እና የነፍጠኛ ርዝራዥ ኣቀንቃኞች መልዕክት : ክፍል ሁለት

Posted by
ጃንዋሪ 16, 2014 | ቃሉ ኩሽ

To Read Part One Click HERE
ክፍል ሁለት
አቶ ተክሌ በጽሁፉም ሆነ በቃለምልልሱ ዉስጥ በግብታዊነትና በደም ፍላት ለኣማራዉ ያስተላለፉት መልዕክት የጦር ጥሪ ሲገመገም ከ19ኛዉ ክፍለዘመን የደብተራዎች አስተሳሰብ በጣም የዘቀጠ ሆኖ የደብተራዎቹ የቆሎ ተማሪ በሚመስል መልኩ ነበር። ለምሳሌ ደጋግሞ ሲናገር የነበረዉ የአማራ አሸናፍነት እና ሞራል ያለዉ መሆኑንና ለዚህም የኦሮሞ ህዝብ እንደሚቀናበትና የአማራ ህዝብ ወደፍት እንደሚያስብና የኦሮሞ ህዝብ ደግሞ ወደኋላ እንደሚያስብ አድርጎ ሲዘባርቅ ነበር። ነገር ግን እንኳን የዛሬ 21ኛዉ ክፍለዘመን ይቅርና በ19ኛዉ ክፍለዘመን ከአዉሮጳዎቹ የእንግሊዝ ተወላጅ ጆን ከምደን ሆቴን (John Camden Hotten) "“Life in the land of Prester John” በሚለዉ መጽሃፉ ዉስጥ እንደሚከተለዉ ነዉ።

The Oromo are noble in appearance, more grave and thoughtful than the Abyssinian, eloquent, strong, and generally handsome; with the pride of a nation of warriors, but very courteous and amenable to reason.” ብሎ ነበር።

በዚሁ መጽሃፉ ዉስጥ ስለአማራዉ ሲገልጽ እንዲህ ነበር ያስቀመጠዉ።

“The manners of the Amhara are pleasing; their features are generally of the European and Asiatic, that is, Arab, cast, and they are remarkably quick. … Their standard of morality is very low; sensual pleasures, as intoxication, are gratified without scruple and without shame:…”

አቶ ተክሌ ደጋግመዉ ሲናገር የነበረዉ ስለአማራ ጀግንነት ነዉ። ለዚህም ጀግንነቱ ሌሎች እንደሚቀኑበት ነበር ያስቀመጠዉ። ነገር ግን ከታሪክ እንደምናዉቀዉ ይህ ህዝብ በጣም ፈሪ፥ ነገር ጎንጓኝ፥ ፍርሃቱን ለመሸፈን ፉከራና እና ቀረርቶ እንደሚያበዛ ነዉ። በመሆኑም አቶ ተክሌ ብዙ የዘላበዱት ያ የለመዱት ፉከራና ለዘመዶቹ ለማስታወስ ነዉ።

ሌላዉ የአቶ ተክሌ ልብወለድ ታሪክ ደግሞ ደጋግሞ የገለጸልን ስለወንድ ልጅ መስለብ ነዉ። ቀደም ሲል ባለፈዉ ጽሁፌ ዉስጥ እንዳቀረብኩት እነዚህ ሰዎች የታሪክ ደሃ መሆናቸዉና የቀድሞ ደብተራዎች የጻፉትን በመድገምና በመደጋገም እስከዛሬ ደርሰዋል።

ለምሳሌ የክዩባ ዜጋና የእስፓንሽ ተወላጅ ኮሎኔል አሌክሳንዴር ዴል ባዩ በ1920 እ.ኤ.ኣ ሬድ ላዮን በሚባለዉ መጽሃፉ ዉስጥ እንዲህ በማለት ኣስፍረዋል።

በጥቁር ምድር ስልብ ሰዉ ያልተለመዱ በርካታ ስራዎች በመስራት ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። ከሚሰጣቸዉ የተለያዩ አገልግሎቶች መሃል የጌታዉን ሴቶች መጠበቅ፥ በቤት ዉስጥ ማጫወት፥ ማዝናናት ጥቂቶች ናቸዉ። በዚህች የኣቢሲንያ ምድር ይህ ስልብ ሰዉ አንድ የሆነ ደረጃና ቦታ ይሰጠዋል። በህብረተሰቡ ዉስጥ ከፍተኛ ቦታ ያላቸዉ የገዥ መደቦች ያዝናናል ያጫዉታል። ስልብ እንደተለየ ፍጡር ወይም ሰዉ ይቆጠራል። ማንንም የማይጎዳ ኣካል ተደርጎ በአገሪቱ ከፍተኛ አዛዦች ዘንድ ይታመናል። ፍጹም ታማኝ ብለዉ ከሚያቀርቧቸዉ አንዱ ነዉ።

አንድ ስልብ ልጅ በዚህ መልኩ የሚያዝበት በኢትዮጲያዉያን ኃላፍዎችና አለቆች ዘንድ የመነጨዉን ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣዉ ስርዐታቸዉ ጋር የተቆራኘ ነዉ። አንድ ስልብ ለማግኘት ዕድለኛ ወይም በኣጋጣሚዉ የተሳካልክ ካልሆንክ በቀር በጣም ከባድ ነዉ። ምክንያቱም መሸለቱ የሚካሄደዉ በአንድ ልምድ ባለዉ የቀዶ ጥገና ባለሙያ ሳይሆን በኣንድ ባሪያ ወይም ጦረኛ ወታደር ነዉ። በጠንካራ እጆቹ ጥንቃቄ በጎደለዉ መልኩ በጭፍኑ በመቁረጥ የሚካሄደዉ የመንደር ዉስጥ ቀዶጥገና በመሆኑ በደም መፍሰስና ቁስሉ በማመርቀዝ ለጉዳት እየዳረጋቸዉ ስለሚሞቱ ይህን ሁሉ አልፎ አንድ ስልብ ማግኘት እድለኛ ያሰኛል።

በመጀመርያ ደረጃ ይህ ሰዉ ከደሃ ቤተሰብ ነዉ። ቤተሰቦቹም ልጃቸዉ ስልብ ሆኖ አገልግሎትን ለመስጠት አንድ ራስ ሲመርጥ ከፍተኛ ኩራትና ክብር ይሰማቸዋል። ለመሰለብ የታጨዉ ወጣት ትንሽ መሆን አለበት። ምክንያቱም አንድ ለአቅመ ኣዳም የደረሰ ልጅ ራሱንና ስለተፈጥሮዉ ካወቀና ስለግብረስጋ ግንኙነት ግንዛቤ ካገኘ እንዲህ ያለዉን ተግባር አይፈጽምም፥ ቂም በመቋጠር ለበቀል ይነሳሳል ብለዉ ያስባሉ።

እንግዲህ ኣበሾች (ኣማሮች) ይህን ጉድ ደብቀዉና፣ የሴትን ልጅ ጡት በመቁረጥ እንደጀግንነት በመቁጠር ጉራ ይነዛሉ። ያዉም በግንባር ዉጊያ ሳይሆን የተማረከዉንና በዋሻ ዉስጥ የተደበቁ ኣቅመደካሞች የሆኑ ሴቶችን፥ ሽማግሌዎችንና ህጻናትን ብሊትና ጡት እንዲሁም እጅ በመቁረጥ ኢሰብ ኣዊ ድርጊት በመፈጸም ነዉ። የሴት ልጅን ጡት በመቁረጥ የሚፎክር ህዝብ ጀግና ነን ብለዉ ሲፎክሩ ያሳፍራል።

ለሁሉም ነገር ለሚደርሰዉ ጥፋት ሁሉ ተጠያቂዉ አቶ ተክሌ የሻዉን የመሰሉ የነፍጠኛ ልጆችና የ21ኛዉ ክፍለዘመን ደብተራዎች ናቸዉ።

ይቀጥላል

No comments:

Post a Comment